የቡኢ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት

gebiwoch_muluken (Small)

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የአቶ ሙሉቀን ቱጂ መልክት

የከተማችን ኢኮኖሚ ከሚያመነጨው  ሀብት የሚገኘውን ገቢ አሟጠን በመሰብሰብ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የህዝባችንን የመልማት ፍላጎት እያሳካን ፣ ለብልፅግና   ጉዟችን ምቹ ሁኔታ እየፈጠርን እንሄዳለን ።

ከተማችን እንደ መዋቅር ራሱን ችሎ ከተደራጀበት ዓመት ጀምሮ ከምንሰበስበው የውስጥ ገቢ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን መመለስና ማሳካት ችለናል፡፡

የሰራናቸው የልማት ስራዎችም በየዓመቱ ተጨማሪ የገቢ እድገት እንዲመጣ ከማድረግ አኳያ የነበረው ሚና ቀላል የሚባል አልነበረም ነገር ግን ከተማችን እያሳየች ካለው የስራ እንቅስቃሴ አንፃር ስንመለከተው እድገቷን በሚመጥን መንገድ የውስጥ ገቢዋን አሟጠን ሰብስበን ለልማት አውለናል ለማለት አያስደፍርም ። በመሆኑም መጠቀም ሲገባን በአግባቡ ሰብስበን ለልማት ያላዋልነው የከተማችን የውስጥ አቅም ለመጨመር የግብር ከፋዮቻችንና መላው የከተማችን ህዝብ አስተዋፅኦ ና ድጋፍ የሚጠይቅ ሲሆን ተቋማችንም ተግባሩን  ለማስፈፀም አዳዲስ ስልቶችንና አሰራሮችን በመከተል በቁርጠኝነት መስራት  ይጠበቅብናል።

"መንግስት በፈጠረው ምቹ ሁኔታ ተጠቅሜ ሰርቼና አትርፌ ከማገኘው  ትርፍ ላይ የምከፍለው ግብር/ታክስ እኔና ሌሎች ወገኖቼ የሚፈልጉት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የሆኑ ችግሮች መፍቻ የሚውል በመሆኑ በታማኝነት ግብር መክፈል አለብኝ፡፡" የሚሉ ግብር ከፋዮችን ቁጥር  እያሳደግን  መሄድ  ቁልፍ  ጉዳያችን ይሆናል ።  ማህበረሰባችን  በግብር/ታክስ ላይ ያለው ግንዛቤና አመለካከት ውስንነት ያለበት በመሆኑ በትምህርትና ስልጠና እያሳደጉ ማስኬድ ፣አውቆ የሚያጭበረብረውን  ደግሞ የታክስ ህግ ማስከበር ስራዎችን ጠንከር አድርገን መስራት እንደሚኖርብን ያስገድደናል፡፡

የከተማችን የገቢ እድገት አስከነችግሩም ቢሆን ስንመለከት በ2015 ዓ.ም ከነበረበት የመደበኛና ማዘጋጃ ቤት ገቢ  68 ሚሊዮን ብር  አንፃራዊ የመሰብሰብ እድገት አሳይቶ  በ2016 ዓ.ም ከ84  ሚሊዮን ብር በላይ ከውስጥ ገቢ ለመሰብሰብ ግብ ተጥሎ  ከ110 % በላይ ማሳካት የተቻለ ሲሆን  ለገቢ እድገቱም  ዋነኛ ተዋንያኖች  የሆኑት የከተማችን ግብር ከፋዮችና መላው ማህበረሰቡን እያመሰገንን በ2017 ዓ/ም  በመደበኛና በመዘጋጃ ቤት ከ 208 ሚሊየን ብር በላይ ሰብስበን ለልማት  ለማዋል አቅደን እየተንቀሳቀስን ሲሆን በቀጣይ የምናስበውንና እያደገ የመጣውን የህዝባችን የመልማት ፍላጎት  በጊዜው መልስ መስጠት እንዲቻል በግብይት ወቅት  ደረሰኝ የመስጠትና የመቀበል ባህላችን አሁን ካለበት ሰፊ ችግር ወጥቶ ስልጣኔ በተሞላበት መንገድ ለፈፀምነው ግዥና ላገኘነው አገልግሎት ህጋዊ ደረሰኝ የመጠየቅና የመቀበል ልምዳችንን ማሳደግ እንዳለብንና በወቅቱ ለልማት መዋል እንዲችል በዓመቱ መጀመሪያ ላይ የአፈር ግብር መክፈላችንን ሳንዘነጋ  የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ  በጋራ ሰርተን በጋራ  እድገት እንድናመጣ የበኩላችንን  ድርሻ እየተወጣን እንሂድ ማለት እፈልጋለሁ ። አመሰግናለሁ !

"የከተማችን የውስጥ የወጪ ፍላጎታችንን በውስጥ ገቢያችን ለመሸፈን እንሰራለን !"

gebiwoch_muluken (Small)

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ቱጂ

ተልእኮ

ከተማዊ፤ ዞናዊ ፤ክልላዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ህብረተሰቡን ለሁለንተናዊ ተሳትፎ የሚያነሳሳ ፤የሚያጎለብትና ተጠቃሚ የሚያደርግ የኮሚዩኒኬሽን ስርዓት በመዘረጋት ተአማኒ እና ጥራቱን የጠበቀ መረጃ ተደራሽ ማድረግ ነው፡፡

ራዕይ

በ2025 ዓም የከተማችን ህዝቦች በላቀ መረጃ በልፅገው የጋራ ውሳኔ ሰጪነታቸው ተረጋግጦ በመካከላቸው እኩልነት፤አንድነትና ወንድማማችነት ተጠናክሮ ማየት

ራዕይ

በ2025 ዓም የከተማችን ህዝቦች በላቀ መረጃ በልፅገው የጋራ ውሳኔ ሰጪነታቸው ተረጋግጦ በመካከላቸው እኩልነት፤አንድነትና ወንድማማችነት ተጠናክሮ ማየት

እሴቶች

  1. ግልጽነትና ክፍት፣
  2. ብዙኃንነትና እኩልነት፣
  3. ተደራሽነት፣ወቅታዊነትና ምላሽ ሰጭነት፣
  4. ሙያዊነትና ፈጠራ፣
  5. ተኣማንነትና ትክክለኛነት፣

ዓላማ

አገልግሎቱ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በርካታ ዓላማዎችን እንደሚያሳካ የሚጠበቅ ሆኖ በዋናነት በሚከተሉት ዓላማዎች ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡እነሱም፡-

  1. በመንግሥት የመረጃና የተግባቦት ወይም ኮሙኒኬሽን ሥርአት የቃል አቀባይነትና ስትራቴጅካዊ የመሪነት ሚና መጫወት፤
  2. መንግሥት ፖሊሲዎች፣ መርሐ ግብሮች፣ ፕሮግራሞችና ዕቅድችን መሠረት ያደረጉ አጀንዳዎችን በማዘጋጀት ቀልጣፋና ውጤታማ የመረጃና የተግባቦት ሥርአትን በመፍጠር ምልዓተ ሕዝቡን ተደራሽ ማድረግና ተሳትፎዉን ማሳደግ፤

  3. በልዩ ልዩ መንግሥት ተቋማት፣ የሚዲያ አዉታሮችና በባለድርሻ አካላት መካከል ውጤታማና ቀልጣፋ የመረጃና የተግባቦት ሥርአትን በመፍጠር ኹሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች ከመንግሥት መረጃ ዕኩል የሚያገኙበትና ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር፤

  4. መንግሥትን ፖሊሲዎች፣ መርሐ ግብሮችና ፕሮግራሞችን መሠረት በማድረግ ኅብረ- ብሔራዊ አንድነትን፣ የሀገር ፍቅርን፣ ሀገራዊ ተግባቦትን፣ የዳሞክራሲ ባህልን ለማጎልበትና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ቀልጣፋና ውጤታማ የመረጃና የተግባቦት ሥርአት ለመዘርጋት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ አመራር መስጠትን ያካተተ ነው፡፡

ተልእኮ

ከተማዊ፤ ዞናዊ ፤ክልላዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ህብረተሰቡን ለሁለንተናዊ ተሳትፎ የሚያነሳሳ ፤የሚያጎለብትና ተጠቃሚ የሚያደርግ የኮሚዩኒኬሽን ስርዓት በመዘረጋት ተአማኒ እና ጥራቱን የጠበቀ መረጃ ተደራሽ ማድረግ ነው፡፡

ራዕይ
በ2025 ዓም የከተማችን ህዝቦች በላቀ መረጃ በልፅገው የጋራ ውሳኔ ሰጪነታቸው ተረጋግጦ በመካከላቸው እኩልነት፤አንድነትና ወንድማማችነት ተጠናክሮ ማየት

ራዕይ

በ2025 ዓም የከተማችን ህዝቦች በላቀ መረጃ በልፅገው የጋራ ውሳኔ ሰጪነታቸው ተረጋግጦ በመካከላቸው እኩልነት፤አንድነትና ወንድማማችነት ተጠናክሮ ማየት

እሴቶች

    1. ግልጽነትና ክፍት፣
    2. ብዙኃንነትና እኩልነት፣
    3. ተደራሽነት፣ወቅታዊነትና ምላሽ ሰጭነት፣
    4. ሙያዊነትና ፈጠራ፣
    5. ተኣማንነትና ትክክለኛነት፣
  1. ዓላማ

አገልግሎቱ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በርካታ ዓላማዎችን እንደሚያሳካ የሚጠበቅ ሆኖ በዋናነት በሚከተሉት ዓላማዎች ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡እነሱም፡-

    1. በመንግሥት የመረጃና የተግባቦት ወይም ኮሙኒኬሽን ሥርአት የቃል አቀባይነትና ስትራቴጅካዊ የመሪነት ሚና መጫወት፤
    2. መንግሥት ፖሊሲዎች፣ መርሐ ግብሮች፣ ፕሮግራሞችና ዕቅድችን መሠረት ያደረጉ አጀንዳዎችን በማዘጋጀት ቀልጣፋና ውጤታማ የመረጃና የተግባቦት ሥርአትን በመፍጠር ምልዓተ ሕዝቡን ተደራሽ ማድረግና ተሳትፎዉን ማሳደግ፤
    3. በልዩ ልዩ መንግሥት ተቋማት፣ የሚዲያ አዉታሮችና በባለድርሻ አካላት መካከል ውጤታማና ቀልጣፋ የመረጃና የተግባቦት ሥርአትን በመፍጠር ኹሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች ከመንግሥት መረጃ ዕኩል የሚያገኙበትና ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር፤
    4. መንግሥትን ፖሊሲዎች፣ መርሐ ግብሮችና ፕሮግራሞችን መሠረት በማድረግ ኅብረ- ብሔራዊ አንድነትን፣ የሀገር ፍቅርን፣ ሀገራዊ ተግባቦትን፣ የዳሞክራሲ ባህልን ለማጎልበትና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ቀልጣፋና ውጤታማ የመረጃና የተግባቦት ሥርአት ለመዘርጋት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ አመራር መስጠትን ያካተተ ነው፡፡

የተቋሙ ተግባርና ሃላፊነት