የቡኢ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት

BUEE2968 (Small)

የተቋሙ ኃላፊ የአቶ ቴዎድሮስ ከበደ መልዕክት

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዩኒት ዋናው አላማ በከተማው የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎቶች በማልማትና ከሌሎች አቅራቢዎች ጋር በመሆን በሁሉም ስፍራ በስፋት በመጠቀም የህብረተሰቡን ኑሮ ማሻሻልና ቴክኖሎጂ ለከተማው እድገት የሚሰጠውን ድጋፍ ማሳደግ ነው፡፡ እንዲሁም ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍን በማሳደግና በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ያለውን አስተዋጽኦ በማጎልበት ከተማችን የፈጣን ልማትና እድገት ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ ነው፡፡

በመሆኑም ዩኒቱ እስከ ቀበሌ ባሉ መንግስታዊ ተቋማት ውስጥ የሚሰጠው አገልግሎት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈና የተደራጀ እንዲሆንና አገልግሎት አሰጣጡ ዘመናዊ ቀልጣፋና ውጤታማ በማድረግ መልካም አስተዳደርን ማስፈንና የሃብት ብክነትን መቀነስ ነው፡፡

በተጨማሪም በህብረተሰቡ ውስጥ ዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂን በመዘርጋትና በማስፋፋት ህብረተሰባችን የግብርና የገበያ፤ የጤና፤ የትምህርት እና የንግድ መረጃዎችን በአቅራቢያው እንዲያገኝ በማድረግ በገጠርና በከተማው ህብረተሰብ መካከል ያለውን የዘመናዊ መረጃ ቴክኖሎጂ ክፍተት ማጥበብ ነው፡፡

በተጓዳኝም ፈጣን እድገት ለማረጋገጥ የግሉ ዘርፍ ቴክኖሎጂውን ለማስፋፋት የሚጫወተውን ሚና ግምት ውስጥ በማስገባት የሚጎለብትበትንና የሚስፋፋበትን መንገድ ማጠናከር አንዱ ዓላማው ነው፡፡

የተቋሙ አጠቃላይ ገጽታ

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት እንዲቋቋም ከነባሩ ዞን በቁጥር ጉዞ/ሳ/ኢ/ቴ/መ17/1/13 በቀን 22/10/2013 ዓ/ም ቢገለፅም ከተማ አሰተዳደሩ በነበረበት የቢሮ እና የበጀት እጥረት ማቋቋም አልተቻለም ሆኖም ከተማ አስተዳደሩ ያለውን በጀት እና ቢሮ ለማብቃቃት ጥረት አድርጎ በ2015 በጀት ዓመት በ3ኛው ሩብ በመጨረሻው ወር ላይ ማቋቋም ችሏል። በዚህም መሰረት የቡኢ ከተማ አስተዳደር ዩኒት የቀድሞው ክልል ባወረደው መመሪያ መሰረት የሳይንስ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ስራዎች ድጋፍና ክትትል እና አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት፣ የኢኮቴ መሰረተ ልማት ዝርጋታና ዳይሬክቶሬት እና የሶፍትዌርና ድህረ-ገፅ ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በአጠቃላይ በሶስት ዋና ዋና ዳይሬክቶሬቶች እና በደጋፊ ዳይሬክቶሬቶች እንዲደራጅ ጥረት ተደርጎ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። በቀጣይም አዲስ በተዋቀረው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሚያወረዳቸው መመሪያዎች መሰረት የአጭር የረጅም ጊዜ ዕቅድ በማቀድ በሀገራችን ከመጣው ለውጥ ጋር ተያይዞ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ለአገልግሎት አሰጣጥ ምቹ ሆነው እንዲደራጁ በተቀመጠዉ አገራዊ አቅጣጫ መሰረት የማሀበረሰባችንን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ ተቋማት ስራቸው በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን ቀደም ሲል ከነበረው ጉራጌ ዞን ሳኢቴ መምሪያ ጋር የነበሩብንን ክፍተቶች በመደፈን አዲስ የተዋቀረው የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሳኢቴ መመሪያ የሚያደርጉልንን ድጋፍ እና ክትትል በመተማመን ወደ ስራ ገብተናል።

BUEE2968 (Small)

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ሳይንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቴዎድሮስ ከበደ

ተልእኮ

በከተማው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋፋት መዋቅራዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነው፡፡

ራዕይ

በ2030 በከተማው ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣የማልማት ፣የመፍጠር ፣የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት፡፡

እሴቶች

  1. በጎ ህሊናና ቅንልቦና፣
  2. የስራ ፍቅር ናትጋት፣
  3. ያልተገደበአስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣
  4. ለለውጥ በጋራ መስራት፤
  5. ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤
  6. ችግርፈቺነት፤
  7. የማይረካ የመማር ጥማት፤
  8. ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣
  9. ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣

ዓላማ

ጽ/ቤቱ የተሰጠውን ኃላፊነትና ተግባር ማለትም በከተማው ዘመናዊ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በመመርመር፣ በመቅዳት፣ በማላመድና ያለዉን አቅም አሟጦ ለመጠቀም የሚያስችል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የመዘርጋትና የማስፋፋት ሥራዎችን በስትራቴጂያዊ አስተሳሰብ ለመምራት፣ በሁሉም ደረጃ ባሉ ፈጻሚዎች መካከል ተግባቦትን ፈጥሮ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የልማትና የለውጥ ዘመን ዕቅድ ያለውን ሥራዎችን ቴክኖሎጂያዊ ድጋፍ መስጠት ነዉ፡፡

በአጠቃላይ በ2016 በጀት ዓመት የነበረን የዕቅድ አፈጻጸም ሁኔታ በመገምገም በጠንካራና በደካማጎን በመለየት የ2016 ድክመት በማረም ጥንካሬ አጎልብተን የዕቅድ አካል በማድረግ ለ2017 በጀት ዓመት የተቀመጡ ስጋቶችን ቀድመን በማወቅ መልካም አጋጣሚዎች እንደ ግብዓት በመጠቀም ባለፉት በ2016 አመታት ያልተፈጸሙትን ተግባራት በሚክስ መልኩ የዳበረ ዕቅድ በማዘጋጀት የየተግባሩን አላማ ለማሳካት ከወትሮው በተሻለ ሁኔታ የመፈጸም ወኔ ሰንቀን መገኘትና ይህንን የሚያረጋግጥ ዕቅድ ማዘጋጀት ይኖርብናል የሚል ስምምነት ላይ በመድረስ ከዚህ በታች ለሰፈረው ለ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ እንደ አስፈላጊነቱተ ወስዷል፡፡.

 

ተልእኮ

በከተማው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋፋት መዋቅራዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነው፡፡

ራዕይ

በ2030 በከተማው ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣የማልማት ፣የመፍጠር ፣የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት፡፡

እሴቶች

  1. በጎ ህሊናና ቅንልቦና፣
  2. የስራ ፍቅር ናትጋት፣
  3. ያልተገደበአስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣
  4. ለለውጥ በጋራ መስራት፤
  5. ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤
  6. ችግርፈቺነት፤
  7. የማይረካ የመማር ጥማት፤
  8. ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣
  9. ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣

ዓላማ

ጽ/ቤቱ የተሰጠውን ኃላፊነትና ተግባር ማለትም በከተማው ዘመናዊ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በመመርመር፣ በመቅዳት፣ በማላመድና ያለዉን አቅም አሟጦ ለመጠቀም የሚያስችል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የመዘርጋትና የማስፋፋት ሥራዎችን በስትራቴጂያዊ አስተሳሰብ ለመምራት፣ በሁሉም ደረጃ ባሉ ፈጻሚዎች መካከል ተግባቦትን ፈጥሮ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የልማትና የለውጥ ዘመን ዕቅድ ያለውን ሥራዎችን ቴክኖሎጂያዊ ድጋፍ መስጠት ነዉ፡፡

በአጠቃላይ በ2016 በጀት ዓመት የነበረን የዕቅድ አፈጻጸም ሁኔታ በመገምገም በጠንካራና በደካማጎን በመለየት የ2016 ድክመት በማረም ጥንካሬ አጎልብተን የዕቅድ አካል በማድረግ ለ2017 በጀት ዓመት የተቀመጡ ስጋቶችን ቀድመን በማወቅ መልካም አጋጣሚዎች እንደ ግብዓት በመጠቀም ባለፉት በ2016 አመታት ያልተፈጸሙትን ተግባራት በሚክስ መልኩ የዳበረ ዕቅድ በማዘጋጀት የየተግባሩን አላማ ለማሳካት ከወትሮው በተሻለ ሁኔታ የመፈጸም ወኔ ሰንቀን መገኘትና ይህንን የሚያረጋግጥ ዕቅድ ማዘጋጀት ይኖርብናል የሚል ስምምነት ላይ በመድረስ ከዚህ በታች ለሰፈረው ለ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ እንደ አስፈላጊነቱተ ወስዷል፡፡.

የተቋሙ ዋና ዋና ተግባራት