የቡኢ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ጽ/ቤት

BUEE2977 (Small)

የተቋሙ ኃላፊ የአቶ ሳምሶን እሼቴ መልዕክት

ፕላንና ልማት ጽ/ቤት የከተማዉን አሰፈፃሚ አከላት እንደገና ለማቋቋምና ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ በቁጥር 199/2015 የተቋቋመ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የፕላንና ልማት ጽ/ቤት በከተማዉ ከተቋቋሙት አስፈጻሚ አካላት አንዱ ሲሆን የተቋቋመበት ዋና ዓላማ የከተማዉን የልማት እንቅስቃሴዎች በዕቅድ እንዲመሩ ለማስቻልና በተግባራት አፈጻጸም ረገድ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት አሠራር ይበልጥ እንዲሰፍን በማድረግ፣ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል እንዲረጋገጥና ዘመናዊ የመረጃ አያያዝና ስርጭት ስርዓት በመዘርጋት የከተማዉን ትክክለኛና ወቅታዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ገጽታ መረጃዎችን በማሰባሰብ ማደራጀትና ለተጠቃሚዎች በማሰራጨት እና የህዝብ ቁጥር ዕድገት ከኢኮኖሚ ዕድገት ጋር ተጣጥሞ እንዲጓዝ በመሥራት ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይ እንዲሆን የሚጠበቅበትን ተልእኮ ለመወጣት ነው፡፡ ባለፉት ዓመታት በሀገራችንም ሆነ በከተማችን በተካሄደው የለውጥ እንቅስቃሴ ህዝቡ በየደረጃው የሚያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በተጠናና በተደራጀ መልክ ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ተግባራዊ የሚደረግ የ10 ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ ሰነድ በከተማዉ የተዘጋጀ ሲሆን የከተማዉን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት በእቅድ ለመምራት የሚያስችል የቀሪ 7 ዓመታት  መሪ የልማት ዕቅድ ሰነድ ተዘጋጅቶ በሚመለከታቸው ውሳኔ ሰጪ አካላት ተተችቶ ከጸደቀ በኃላ  ተግባራዊ በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ከዓመት ዓመት በሚሊዩኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለካፒታል ፕሮጀክቶች በመመደብ በርካት የመሰረተ ልማት ሥራዎች እየገነባ ይገኛል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ህዝብ የተገነቡ መሰረተ ልማቶች በባለቤትነት እንዲጠብቅና እንዲንከባከባቸዉ የበኩሉን አስተዎፆ አንዲያደርግ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ፡፡

BUEE2977 (Small)

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ፕላን እና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሳምሶን እሼቴ

ተልእኮ

ግልፀኝነትና ተጠያቂነት በሰፈነበት አሰራር ዘመናዊ የልማት ዕቅድና መረጃ፣ በመዘርጋት፣ የልማት አጋሮችን በማስተባበርና የሕዝብ ቁጥር ዕድገት ከኢኮኖሚ እድገት ጋር እንዲጣጣም በመስራት በከተማዉ ፈጣንና ቀጣይነት ያለው  ልማት እንዲረጋገጥ ማስቻል፡፡

ራዕይ

ፍትሃዊ የሀብት ድልድልና አጠቃቀም በማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኀበራዊ ዕድገትን በማስፈን የከተማዉ ሕዝብ ከድህነት ተላቆ "ኢትዮጵያ አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት" ሀገራዊ ራዕይ ተሳክቶ ማየት፡፡

እሴቶች

  1. ቆጣቢነት
  2. ወቅታዊና አስተማማኝ መረጃ
  3. ፍትሃዊነት
  4. ውጤታማነት
  5. ግልፀኝነትና ተጠያቂነት
  6. ተቆርቋሪነት
  7. ቀልጣፋ አገልገሎት
  8. በእቅድ መመራት
  9. ሕጋዊነት

ተልእኮ

ግልፀኝነትና ተጠያቂነት በሰፈነበት አሰራር ዘመናዊ የልማት ዕቅድና መረጃ፣ በመዘርጋት፣ የልማት አጋሮችን በማስተባበርና የሕዝብ ቁጥር ዕድገት ከኢኮኖሚ እድገት ጋር እንዲጣጣም በመስራት በከተማዉ ፈጣንና ቀጣይነት ያለው  ልማት እንዲረጋገጥ ማስቻል፡፡

ራዕይ

ፍትሃዊ የሀብት ድልድልና አጠቃቀም በማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኀበራዊ ዕድገትን በማስፈን የከተማዉ ሕዝብ ከድህነት ተላቆ "ኢትዮጵያ አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት" ሀገራዊ ራዕይ ተሳክቶ ማየት፡፡

እሴቶች

  1. ቆጣቢነት
  2. ወቅታዊና አስተማማኝ መረጃ
  3. ፍትሃዊነት
  4. ውጤታማነት
  5. ግልፀኝነትና ተጠያቂነት
  6. ተቆርቋሪነት
  7. ቀልጣፋ አገልገሎት
  8. በእቅድ መመራት
  9. ሕጋዊነት

የተቋሙ ተግባርና ሃላፊነት

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በቡኢ ከተማ አስተዳደር ጊዜያዊ አማካሪ ምክር ቤት ተጀምረዉ ሳይጠናቀቁ ላደሩና ለአዳዲስ ካፒታል ፕሮጀክቶች 49,272,040 ብር በማፀደቅ በርካታ መሰተ ልማቶች መገንባት ተችሏል፡፡ ከተሰሩት በርካታ ካፒታል ፕሮጀክቶች ዉስጥ ለአብነት የጤና ጣቢያ ግንባታ ተጨማሪ ብሎኮች ግንባታ፣ ዲች ግንባታ፣ ካልቨርትና ፕሪካስት ግንባታ፣ አረንጓዴ መናፈሻ አጥር ግንባታ፣ ከተማ አስተዳደሩ የራሱን ኳሪሲ ሳይት እንዲኖረዉ ካሳ በመክፈል ባለቤት ሆኗል በዚህም በርካታ ሜ/ኪ የገረጋንቲ ምርት ማምረት ተችሏል፣የነጌሳ ቀበሌ መብራት ተጠቃሚ እንዲሆን የመብራት ዝርጋታ ወጪ ግምት ለመብራት አገልግሎት ዲስትሪክት 100% ተከፍሏል፣ ለመጠጥ ዉሃ ግንባታ ያለበትንና የሚጠበቅበትን የማችንግ ፈንድ ገንዘብ 100% ከፍሏል ግንባታዉ ከነበረበት ችግር በፍጥነት አሰፈላጊዉን ዉሳኔ እንደ ከተማ አስተዳደር በመወሰን ከችግር በማዉጣት የሲቪል ሥራዉና ቧንቧ ዝርጋታ በማጠናቀቅ ወደ ኤሌክትሮ መካኒካል ስራ ማስጀመርና ማፋጠን ተችሏል፣ለአዳሪ ት/ቤት ግንባታ የሚዉል 10 ሄ/ር መሬት ተገቢዉን ካሳ አስራ ሚሊዩን ብር የሚቆጠር በመክፈል ከይገባኛል ነፃ የማድረግ ሥራ ተሰርቷል፡፡