ተልእኮ
የከተማ አስተዳደሩ አስራርና አደረጃጀት ዘመናዊ በማድረግ ግጭትን፣የሀይማኖት አክራሪነት በብቃት ለመከላከል የሚያስችል የፀጥታ መረጃ ስርዓት በመፍጠር በህ/ሰቡ ንቁ ተሳትፎ የሚታገዝ የፀጥታ አስከባሪ ሀይል እንዲኖር በማድረግ የህግ ታራሚዎችንና የዜጎችን ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን በማስጠበቅ ሰላምና ፀጥታን ማስከበር፡፡
ራዕይ
የዜጎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችና ነፃነቶች ማስከበር፣ሰላምና ፀጥታ ማስፈን፣የህግ የበላይነትና መልካም አስተዳደር የተረጋገጠበት ከተማ አስተዳደር እንዲሆን የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋፆ የሚያበረክት ተቋም ሆኖ ማየት፡፡
እሴቶች
- የሕብረተሰቡን ፀጥታና ደህንነት ማስጠበቅ ተግባራችን ነው
- ለህግ የበላይነት ቆመናል
- ፍትሀዊነት ታማኝነት መለያችን ነው
- የህዝብ አገልጋይነት መርሀችን ነው
- ግልፅነትና ተጠያቂነት መታወቂያችን ነው
- አሳታፊነት መርሀችን ነው
- ሚስጥር መጠበቅ ቃል ኪዳናችን ነው
በከተማችን ሰላምና ፀጥታ በማስፈን መሰረታዊ የህዝባዊ እሴቶቻችን ተቋማዊና በተደራጀ መንገድ ከዘመናዊ አሰራሮች ጋር አቀናጅቶ የመምራትና የማስተባበር ስልጣን በአዋጅ የተሰጠው ለሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ነው፡፡
ተግባር ፡- ጽ/ቤቱ የተቋቋመለትን ዋና ዓላማ ለማሳካት የከተማውን ሰላም፣ፀጥታና ደህንነት አስተማማኝ ደረጃ ለማድረስና የዜጎች ሰብሀዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ በማድረግ ቀጣይነት ያለው ልማትና የመልካም አስተዳደር ለማስፈን የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
አደረጃጀት ፡- አደረጃጀቱም የከተማ አስተዳደር የፖሊስ ጽ/ቤት እና በጽ/ቤቱ በስር ያሉ ዋና ዋና የስራ ሂደቶች እና በመንደር ደረጃ ያሉ የሠላምና ፀጥታ አደረጃጀቶች እና ደጋፊ ስራ ሂደቶችን ጨምሮ የተቋቋመ ተቋም ነው፡፡