የቡኢ ከተማ አስተዳደር ሰራተኛና ማህበራዊ ዩኒት

BUEE2984 (Small)

የተቋሙ ኃላፊ የአቶ ሞላ ታደሰ መልዕክት

ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር የ2017 ዓመት የዳይሬክቶሬቱ ዕቅድ ተዘጋጅቷል፡፡

ዕቅዱ የቁልፍ ተግባራት እና የአበይት ተግባራት በከተማ  ደረጃ የማህበራዊ ጥበቃ ሥርዓት በየደረጃው በመዘርጋት፣ የማህበራዊ ደህንነት አገልግሎቶች ተደራሽነትን በማስፋፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷቸው የሚከናወኑ ተግባራት ይሆናሉ፡፡

ዕቅዱ አምስት ክፍሎች ሲኖሩት በክፍል አንድ የዕቅዱ መነሻ ሁኔታዎች፤ በክፍል ሁለት የዝግጅት፣ የትግበራ እና የማጠቃለያ ምዕራፎች በክፍል ሦስት የበጀት ዓመቱ ግቦችና ዋና ዋና ተግባራት፣ በክፍል አራት የአፈፃፀም ክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ እንዲሁም በክፍል አምስት የዕቅዱ መርሀ-ግብር ተካትቶ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

BUEE2984 (Small)

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ዩኒት አስተባባሪ አቶ ሞላ ታደሰ

ተልእኮ

የሥራ ስምሪት አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የኢንዱስትሪ ሠላም እንዲሰፍን፣ የሠራተኛው ጤንነትና ደህንነት እንዲጠበቅ፣ የሥራ አካባቢዎች እንዲሻሻሉና የዜጐች ማህበራዊ ጥበቃ አገልግሎት (የአካል ጉዳተኞች ዕኩል እድልና ሙሉ ተሳታፊነት እንዲረጋገጥ፣ አረጋውያን ድጋፍና እንክብካቤ እንዲያገኙና ተሳትፎአቸው እንዲጐለብት፣ በልዩ ልዩ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ምክንያት በድህነት፣ ተጋላጭነትና መገለል ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች የተለያዩ ድጋፎች) እንዲያገኙ ማድረግ የሴክተሩ ተልዕኮዎቹ ናቸው፡፡
ራዕይ

በ2022 የኢንዱስትሪ ሠላም ያሰፈነ፣ የሥራ ዕድሎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነትና የማህበራዊ ደህንነት ልማትን ያጐለበተ ሞዴል ሴክተር ሆኖ ማየት

እሴቶች

  1. የኢንዱስትሪ ሰላም ማስፈን
  2. ማህበራዊ ደህንነትን ማስጠበቅ
  3. ለጾታ እኩልነትና ለአካል ጉዳተኞች ሙሉ ተሳትፎ ጠንክረን መስራት
  4. ለአረጋውያን እንክብካቤና ድጋፍ ትኩረት መስጠት
  5. የትብብር፤ የጋራ መግባባት የተቀናጀ አሰራርና የአሳታፊነት መርህ መከተል
  6. ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን መከላከልና መቆጣጠርን የሁሌም ስራዎቻችን አካል አድርገን መስራት
  7. የላቀ አገልግሎት
  8. የአካባቢ ጥበቃና ለተመጣጠነ የህዝብ ቁጥር እድገት መኖር ትኩረት ሰጥተን መስራት

ተልእኮ

የሥራ ስምሪት አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የኢንዱስትሪ ሠላም እንዲሰፍን፣ የሠራተኛው ጤንነትና ደህንነት እንዲጠበቅ፣ የሥራ አካባቢዎች እንዲሻሻሉና የዜጐች ማህበራዊ ጥበቃ አገልግሎት (የአካል ጉዳተኞች ዕኩል እድልና ሙሉ ተሳታፊነት እንዲረጋገጥ፣ አረጋውያን ድጋፍና እንክብካቤ እንዲያገኙና ተሳትፎአቸው እንዲጐለብት፣ በልዩ ልዩ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ምክንያት በድህነት፣ ተጋላጭነትና መገለል ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች የተለያዩ ድጋፎች) እንዲያገኙ ማድረግ የሴክተሩ ተልዕኮዎቹ ናቸው፡፡
ራዕይ

በ2022 የኢንዱስትሪ ሠላም ያሰፈነ፣ የሥራ ዕድሎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነትና የማህበራዊ ደህንነት ልማትን ያጐለበተ ሞዴል ሴክተር ሆኖ ማየት

እሴቶች

  1. የኢንዱስትሪ ሰላም ማስፈን
  2. ማህበራዊ ደህንነትን ማስጠበቅ
  3. ለጾታ እኩልነትና ለአካል ጉዳተኞች ሙሉ ተሳትፎ ጠንክረን መስራት
  4. ለአረጋውያን እንክብካቤና ድጋፍ ትኩረት መስጠት
  5. የትብብር፤ የጋራ መግባባት የተቀናጀ አሰራርና የአሳታፊነት መርህ መከተል
  6. ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን መከላከልና መቆጣጠርን የሁሌም ስራዎቻችን አካል አድርገን መስራት
  7. የላቀ አገልግሎት
  8. የአካባቢ ጥበቃና ለተመጣጠነ የህዝብ ቁጥር እድገት መኖር ትኩረት ሰጥተን መስራት

የተቋሙ ተግባርና ሃላፊነት